በአእምሯችሁ መታደስ ተለወጡ

ወደ ሮሜ 12
2፤ የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።

መለወጥ ማለት ምን ማለት ነው? ሁላችንም መለወጥና ጌታን ደስ ማሰኘት እንፈልጋለን:: ግን እንዴት?!

የማርቆስ ወንጌል 6
35፤ በዚያን ጊዜም ብዙ ሰዓት ካለፈ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው፦ ቦታው ምድረ በዳ ነው አሁንም መሽቶአል፤36፤ የሚበሉት የላቸውምና በዙሪያ ወዳሉ ገጠሮችና መንደሮች ሄደው እንጀራ ለራሳቸው እንዲገዙ አሰናብታቸው፡ አሉት።37፤ እርሱ ግን መልሶ፦ እናንተ የሚበሉትን ስጡአቸው፡ አላቸው። ሄደን እንጀራ በሁለት መቶ ዲናር እንግዛላቸውን? እንዲበሉም እንስጣቸውን? አሉት።38፤ እርሱም፦ ስንት እንጀራ አላችሁ? ሂዱና እዩ፡ አላቸው። ባወቁም ጊዜ፦ አምስት፥ ሁለትም ዓሣ፡ አሉት።39፤ ሁሉንም በየክፍሉ በለመለመ ሣር ላይ እንዲያስቀምጡአቸው አዘዛቸው።

ታሪኩን እናውቃለን አምስት እንጀራና ሁለት ዓሣ ለአምስት ሺህ ሰዎች ተመግበው አስራ ሁለት መሶብ እንደተረፈ እናውቃለን:: ይህ እንዴት ሆነ? ጌታ እኮ አመስግኖ አምስቱን እንጀራ ለአስራ ሁለት አካፍሎ መሶባቸው ላይ ከግማሽ እንጀራ ያልበለጠ ነው እንዲያድሉ የደረሳቸው ሐዋርያቱ:: እስኪ እዚህጋ ቆም ብለን እናስብ አምስት ሺህ ሰው ለመብላት ቁጭ ብሎ ይጠብቃሉ ሐዋርያቱ እጅ የገባው እንጀራ ደግሞ ቁራሽ ነው:: እናስተውል ጌታ ወደ ሰማይ አይቶ ባርኮ ሲሰጣቸው መሶቡን ሞልቶ ፈሰሰ አይለንም ወይም ደግሞ ከክብደቱ የተነሳ አንገዳገዳቸው ወይም ይህንን የመሰለ ነገር አልተጻፈም ስለዚህ ሐዋርያት እየተያዩ እንግዲህ ፊታችን ላለው ሰው ሰተን እንመለስ ብለው ለማደል ተነሱ::

እኔና እናንተ ምን እናደርግ ይሆን? ከነሱ የተሻለ ምክር አንመክርም ቁራሽ ለማቃመስ እንኳን ከባድ ነው ብዙ ገንዘብም ይጠይቃል ብለን እንደመድም ነበር:: ምክንይቱም አእምሮአችን የለመደው የራሱ የአስተሳሰብ ዘይቤ አለ ህብረተሰቡም በዙሪያችን ያለው የተፈጥሮ እውነት ወደ አንድ አቅጣጫ ነው የሚመሩን ስለዚህ እሱን ብቻ ነው የምንከተለው ከዚህ ወጣ ካለብን ይከብደናል ወይም ስህተት ነው እንላለን::

ጌታ እየሱስ የሚያደርገውን ያውቅ ነበርና ሊፈትነው ነበር ፊልጶስን የጠየቀው:: ያንን ቁራሽ እንጀራ እፊት ላለው ግለሰብ ሰተው ተመልሰው ለመቀመጥ ነበር የሄዱት ሐዋርያት ግን ልክ ሰተው ዞር ሲሉ የሚቀጥለው ቁራሽ ይቀመጥ ነበር መሶቡ ላይ:: ታድያ በአስተሳሰባችንን ካልተለወጥንና ጌታ እንደሚያይ ካላየን እመኑኝ ተአምራትን የማየት ተስፋችን የተመናመነ ነው በሌላ አባባል ከባድ ነው የሚሆንብን:: ስለዚህ ነገሮችን ጌታ እንደሚያይ እንይና ቃሉን ስናነብ ከቃሉ ተአምራትን ለማየት ይሁን:: ስንት ነገር ላይ እንድንወጣና እንድናደርግ ጌታ ተናገረን ብለን ቁራሽዋ እንጀራ ስትሰጠን ምን ትሰራለች ኢቺ ብለን የእንጀራ ክምር ለምንጠብቅ ሁሉ ይህ የአእምሮ መለወጥ ካልገባን በስተቀር ችግር ላይ እንደሆንን እንወቅ:: ተአምራትንም ማየት ሆነ ጌታንም በቅጡ ማገልገል ይከብደናል:: አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ካላስቀመጥን በስተቀር ይፈነዳል:: እጅ የምታክለው ደመና ምን አይነት ዝናብ እንደወጣው እናውቃለን እኛም እንደዚሁ ጌታ የሚሰራውን ለማወቅ አስተሳሰባችን መለወጥ አለበት:: ሐዋርያት ይህንን የሚያክል ተአምር ቢያዩም እንኳን በማርቆስ ወንጌል 6: 52 ላይ ቃሉ ‘ስለ እንጀራው አላስተዋሉምና፤ ነገር ግን ልባቸው ደንዝዞ ነበር።’ ይላል ስለዚህ የእግዚአብሔር ጉብኝት አይለፈን ልባችንን በመንገዳችን ላይ እናድርግ::

እግዚአብሔር ይርዳን! አሜን!

Published by Betty & Abera

We’re dedicated to share God’s goodness and mercy through His word!

One thought on “በአእምሯችሁ መታደስ ተለወጡ

Leave a comment